Telegram Group & Telegram Channel
ሰቀሉህ !!!

አንተስ ሁሉን ስታውቅልን ለራስህ አላውቅ ብለህ በዳይህን እንዴት ትፈጥራለህ ? እኛን የሚያዋድደን አለማወቅ ፣ አለመተዋወቅ ነው ። አንተ ብቻ አውቀህ ትወደናለህ ። ሰቀሉህ መልኬ ያልካቸው ፣ ዝቅ ብለህ ከአፈር ያነሣሃቸው ፣ ሬሳቸውን በአፍህ እስትንፋስ ሕያው ያደረግህላቸው ፣ ሚሊየን ጊዜ አድርገህላቸው አንድ ምስጋና የማያውቁ እነዚያ የአዳም ዘሮች ሰቀሉህ ። አንተ ለሁሉ እንደ ተሰቀልህ ፣ አንተን ሁሉ ሰቀለህ ። ከነጻነት ጋር የፈጠርሃቸው እነርሱ የግርግሪት አሰሩህ ። ካንተ በርባንን መረጡ ፣ አልጋ ስትሰጣቸው አመድ ላይ ተንከባለሉ ። የማይፈርድ ችሎት ፣ እውነትን የማይሻ ሸንጎ አቋቁመው ፣ ፍርድ ቤት አድርሰነዋል ለማለት አደባባይ አቆሙህ ። ስለመግደልህ ሳይሆን ስለመፈወስህ ሞት በየኑብህ ። አንተም አርፈህ አልቀመጥ ፣ ሲጠሉህ አልጠላችሁም ብለህ ይኸው ሰቀሉህ !

የሚደበድባትን ባል ያፈቅረኛል የምትል ሚስት ፣ የሚለመጥጠውን ንጉሥ ቆራጥ መሪ የሚል ሕዝብ ባለበት ዓለም በትዕግሥትህ ምክንያት ሰቀሉህ ። ገራፊ የለመደው ወገን የምትገረፍለትን አንተን መቀበል አቃተው ፣ ዛሬም አስመሳዮች ጌታን ተቀበልን እያሉ ራሳቸውን በመቀበል ፣ የተሰቀልከውን ሳይሆን ምቾታቸውን በማሳደድ ይሰቅሉሃል ። አንተም እንቢ አልክ ሁለት ሺህ ዓመት ልብ አልገዛም ብለህ በየጓዳው ፣ በየምርጫው ይሰቅሉሃል ። አይሁድ ስለሰቀሉህ የሚያለቅሱ ደጋግመው በክፋታቸው የሚሰቅሉህ ግብዞች ባሉበት ዓለም አንተ ተሰቀልህ ። ለሰቀሉህ ተሰቀልህላቸው ። ለገደሉህ ሞታቸውን ወሰድህላቸው ። የታመመ ቢታመሙለት አይድንም ። የሞተ ቢሞቱለት ቀና አይልም ። አንተ ግን በመገረፍህ ቍስል የምታድን ፣ በሞትህ ሕይወት የምትሰጥ ነህ ። ይገርማል ሥጋዬን ብሉ ስላልህ ላይበሉህ ሰቀሉህ ። አንተ ግን ሰቀሉኝ አላልህም ፣ ተሰቀልሁላቸው አልህ አንጂ ።

ባንተ ምክንያት ከስንቱ ልጣላ ። ከዙፋን በረትን ፣ ከሰማይ አፈርን መርጠህ በመምጣትህ በር ዘጉብኝ አትበል ። ፍጥረተ ዓለሙን አንዱን በእንጀራ ፣ አንዱን በምስጋና እያጠገብህ የምትኖረው የብላቴናዋን የድንግልን ወተት የለመንከው እኮ ምን ቸግሮህ ነው ! ጠላት የሚፋንንብኝ ባልችል ፣ ድህነት የሚጎስመኝ ቢሳነኝ ነው ። አንተ ግን ወዶ ገብ ድሀ ለምን ሆንህ ! እኮ ከመውደድ አያርፍም ፣ በመጥላት ይራቀን ብለው ሰቀሉህ ። አንተ ግን ሞኝ ሆነህ ሳይሆን አፍቅረህ ፣ መላ አጥተህ ሳይሆን መለኛ ሆነህ ሰቀሉህ ! የባለጠጋው ልጅ ድህነትን ፈቅደህ ተቀበልከው ። ሰውን ለማዳን ሰው ልሁን ብለህ መጣህ ። ሰው ሳይሆኑ ሰውን ለማዳን የሚነሡ ብዙዎች አሉና ልታስተምራቸው ፣ ለሰው ከመሰቀል በፊት ሰው መሆን ይቀድማል ልትላቸው ሰው ሆነህ መጣህ ። የክፋት ብርድ ልብሳቸውን በትምህርት ገፈፍካቸውና ተው ስልህ ይኸው ሰቀሉህ !

የአብ ልጅ ፣ የድንግል ልጅ ያንተ ሞት ግሩም ነው ። በአንድ ዓይን እያስለቀሰ ፣ በአንድ ዓይን የሚያስቅ ነው ። በሚኖርበት ዕድሜ የሚሞቱት ቀዘባዎች ፣ መለሎዎች ፣ ሙናዎች በኀዘን ሰብረውን እንዳይኖሩ አንተ በሠላሳ ሦስት ዓመትህ ሰቀሉህ ። ከሞቱ ያሟሟቱ እያሉ በአደባባይ ለሚወድቁት የሚያለቅሱ አሉና አንተ በአደባባይ በመሰቀል ተጽናኑ አልህ ። ሟች ሁሉ ልብስ አይገፉትም ፣ ለመገነዣም አዲስ ልብስ ይሰፋለታል ። አንተን ግን ልብስህን ገፍፈው ሰቀሉህ ። እነርሱ እኮ ምን ያድርጉ ! ብቻቸውን በር ዘግተው የሚበሉ ናቸው ፤ አንተ አምስት ሺህ ሰው ትመግባለህ ። ሐኪም ቤቱን ልታራቁት በነጻ ትፈውሳለህ ። ባንተ ምክንያት ምግብ ቤቶች ፣ ሸክላ የሚያበሉ ጨካኝ ነጋዴዎች ገቢያቸው ቀነሰ ። አዎ ሰቀሉህ ! እንዲሰቅሉህ ስለፈቀድህላቸው ሰቀሉህ ። መስቀል የቻሉ ትንሣኤህን ማገድ አልቻሉም ።

ዛሬም ድሀ እየበደሉ ፣ ፍርድ እያጓደሉ ፣ ለወንድም መርዝ እየበጠበጡ ይሰቅሉሃል ። አንተ ስለሁሉ በሞትህበት ዓለም ሁሉ አንድ ሰውን ተባብረው ይሰቅሉታል ፣ በድንጋይ ይወግሩታል ። የደቦ ፍርድ ይሰጡታል ። ኦ ምንድነው የምትፈልገው ከእኔ ፣ እስቲ ተወኝ ! እኮ ብያለሁ ዛሬም ሰቀሉህ !!!

የእናትህ ዘመዶች ሰቀሉህ ። እኮ እርሷስ ላንተ ታልቅስ ወይስ ዘመድ ትቀየም ! ቅያሜው እንዲቀር በመስቀል ላይ ይቅር አልህ ! ልቅሶው እንዲሻር ከሞት ተነሣህ ። አንተ ብሩህ ኮከብ ፣ ላያጠፉህ የመቱህ አማኑኤል ሆይ ብቻህን አትነሣ ፣ እኛንም ይዘህ ተነሣ ! ማር ኢየሱስ ጣፋጭ ነህ ! ማር ኢየሱስ መሐሪ ነህ ! የአፍሪካ ቀንድ ላይ ተቀምጠን ጦርነት አላጣ ያለን ሕዝቦችህን የተሰቀልኸው እባክህ ሰላም ስጠን !



ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም.



tg-me.com/Nolawii/3928
Create:
Last Update:

ሰቀሉህ !!!

አንተስ ሁሉን ስታውቅልን ለራስህ አላውቅ ብለህ በዳይህን እንዴት ትፈጥራለህ ? እኛን የሚያዋድደን አለማወቅ ፣ አለመተዋወቅ ነው ። አንተ ብቻ አውቀህ ትወደናለህ ። ሰቀሉህ መልኬ ያልካቸው ፣ ዝቅ ብለህ ከአፈር ያነሣሃቸው ፣ ሬሳቸውን በአፍህ እስትንፋስ ሕያው ያደረግህላቸው ፣ ሚሊየን ጊዜ አድርገህላቸው አንድ ምስጋና የማያውቁ እነዚያ የአዳም ዘሮች ሰቀሉህ ። አንተ ለሁሉ እንደ ተሰቀልህ ፣ አንተን ሁሉ ሰቀለህ ። ከነጻነት ጋር የፈጠርሃቸው እነርሱ የግርግሪት አሰሩህ ። ካንተ በርባንን መረጡ ፣ አልጋ ስትሰጣቸው አመድ ላይ ተንከባለሉ ። የማይፈርድ ችሎት ፣ እውነትን የማይሻ ሸንጎ አቋቁመው ፣ ፍርድ ቤት አድርሰነዋል ለማለት አደባባይ አቆሙህ ። ስለመግደልህ ሳይሆን ስለመፈወስህ ሞት በየኑብህ ። አንተም አርፈህ አልቀመጥ ፣ ሲጠሉህ አልጠላችሁም ብለህ ይኸው ሰቀሉህ !

የሚደበድባትን ባል ያፈቅረኛል የምትል ሚስት ፣ የሚለመጥጠውን ንጉሥ ቆራጥ መሪ የሚል ሕዝብ ባለበት ዓለም በትዕግሥትህ ምክንያት ሰቀሉህ ። ገራፊ የለመደው ወገን የምትገረፍለትን አንተን መቀበል አቃተው ፣ ዛሬም አስመሳዮች ጌታን ተቀበልን እያሉ ራሳቸውን በመቀበል ፣ የተሰቀልከውን ሳይሆን ምቾታቸውን በማሳደድ ይሰቅሉሃል ። አንተም እንቢ አልክ ሁለት ሺህ ዓመት ልብ አልገዛም ብለህ በየጓዳው ፣ በየምርጫው ይሰቅሉሃል ። አይሁድ ስለሰቀሉህ የሚያለቅሱ ደጋግመው በክፋታቸው የሚሰቅሉህ ግብዞች ባሉበት ዓለም አንተ ተሰቀልህ ። ለሰቀሉህ ተሰቀልህላቸው ። ለገደሉህ ሞታቸውን ወሰድህላቸው ። የታመመ ቢታመሙለት አይድንም ። የሞተ ቢሞቱለት ቀና አይልም ። አንተ ግን በመገረፍህ ቍስል የምታድን ፣ በሞትህ ሕይወት የምትሰጥ ነህ ። ይገርማል ሥጋዬን ብሉ ስላልህ ላይበሉህ ሰቀሉህ ። አንተ ግን ሰቀሉኝ አላልህም ፣ ተሰቀልሁላቸው አልህ አንጂ ።

ባንተ ምክንያት ከስንቱ ልጣላ ። ከዙፋን በረትን ፣ ከሰማይ አፈርን መርጠህ በመምጣትህ በር ዘጉብኝ አትበል ። ፍጥረተ ዓለሙን አንዱን በእንጀራ ፣ አንዱን በምስጋና እያጠገብህ የምትኖረው የብላቴናዋን የድንግልን ወተት የለመንከው እኮ ምን ቸግሮህ ነው ! ጠላት የሚፋንንብኝ ባልችል ፣ ድህነት የሚጎስመኝ ቢሳነኝ ነው ። አንተ ግን ወዶ ገብ ድሀ ለምን ሆንህ ! እኮ ከመውደድ አያርፍም ፣ በመጥላት ይራቀን ብለው ሰቀሉህ ። አንተ ግን ሞኝ ሆነህ ሳይሆን አፍቅረህ ፣ መላ አጥተህ ሳይሆን መለኛ ሆነህ ሰቀሉህ ! የባለጠጋው ልጅ ድህነትን ፈቅደህ ተቀበልከው ። ሰውን ለማዳን ሰው ልሁን ብለህ መጣህ ። ሰው ሳይሆኑ ሰውን ለማዳን የሚነሡ ብዙዎች አሉና ልታስተምራቸው ፣ ለሰው ከመሰቀል በፊት ሰው መሆን ይቀድማል ልትላቸው ሰው ሆነህ መጣህ ። የክፋት ብርድ ልብሳቸውን በትምህርት ገፈፍካቸውና ተው ስልህ ይኸው ሰቀሉህ !

የአብ ልጅ ፣ የድንግል ልጅ ያንተ ሞት ግሩም ነው ። በአንድ ዓይን እያስለቀሰ ፣ በአንድ ዓይን የሚያስቅ ነው ። በሚኖርበት ዕድሜ የሚሞቱት ቀዘባዎች ፣ መለሎዎች ፣ ሙናዎች በኀዘን ሰብረውን እንዳይኖሩ አንተ በሠላሳ ሦስት ዓመትህ ሰቀሉህ ። ከሞቱ ያሟሟቱ እያሉ በአደባባይ ለሚወድቁት የሚያለቅሱ አሉና አንተ በአደባባይ በመሰቀል ተጽናኑ አልህ ። ሟች ሁሉ ልብስ አይገፉትም ፣ ለመገነዣም አዲስ ልብስ ይሰፋለታል ። አንተን ግን ልብስህን ገፍፈው ሰቀሉህ ። እነርሱ እኮ ምን ያድርጉ ! ብቻቸውን በር ዘግተው የሚበሉ ናቸው ፤ አንተ አምስት ሺህ ሰው ትመግባለህ ። ሐኪም ቤቱን ልታራቁት በነጻ ትፈውሳለህ ። ባንተ ምክንያት ምግብ ቤቶች ፣ ሸክላ የሚያበሉ ጨካኝ ነጋዴዎች ገቢያቸው ቀነሰ ። አዎ ሰቀሉህ ! እንዲሰቅሉህ ስለፈቀድህላቸው ሰቀሉህ ። መስቀል የቻሉ ትንሣኤህን ማገድ አልቻሉም ።

ዛሬም ድሀ እየበደሉ ፣ ፍርድ እያጓደሉ ፣ ለወንድም መርዝ እየበጠበጡ ይሰቅሉሃል ። አንተ ስለሁሉ በሞትህበት ዓለም ሁሉ አንድ ሰውን ተባብረው ይሰቅሉታል ፣ በድንጋይ ይወግሩታል ። የደቦ ፍርድ ይሰጡታል ። ኦ ምንድነው የምትፈልገው ከእኔ ፣ እስቲ ተወኝ ! እኮ ብያለሁ ዛሬም ሰቀሉህ !!!

የእናትህ ዘመዶች ሰቀሉህ ። እኮ እርሷስ ላንተ ታልቅስ ወይስ ዘመድ ትቀየም ! ቅያሜው እንዲቀር በመስቀል ላይ ይቅር አልህ ! ልቅሶው እንዲሻር ከሞት ተነሣህ ። አንተ ብሩህ ኮከብ ፣ ላያጠፉህ የመቱህ አማኑኤል ሆይ ብቻህን አትነሣ ፣ እኛንም ይዘህ ተነሣ ! ማር ኢየሱስ ጣፋጭ ነህ ! ማር ኢየሱስ መሐሪ ነህ ! የአፍሪካ ቀንድ ላይ ተቀምጠን ጦርነት አላጣ ያለን ሕዝቦችህን የተሰቀልኸው እባክህ ሰላም ስጠን !



ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 25 ቀን 2016 ዓ.ም.

BY Nolawi ኖላዊ


Warning: Undefined variable $i in /var/www/tg-me/post.php on line 283

Share with your friend now:
tg-me.com/Nolawii/3928

View MORE
Open in Telegram


Nolawi ኖላዊ Telegram | DID YOU KNOW?

Date: |

Newly uncovered hack campaign in Telegram

The campaign, which security firm Check Point has named Rampant Kitten, comprises two main components, one for Windows and the other for Android. Rampant Kitten’s objective is to steal Telegram messages, passwords, and two-factor authentication codes sent by SMS and then also take screenshots and record sounds within earshot of an infected phone, the researchers said in a post published on Friday.

Importantly, that investor viewpoint is not new. It cycles in when conditions are right (and vice versa). It also brings the ineffective warnings of an overpriced market with it.Looking toward a good 2022 stock market, there is no apparent reason to expect these issues to change.

Nolawi ኖላዊ from ua


Telegram Nolawi ኖላዊ
FROM USA